Wednesday, April 26, 2017

የዘመኑ ሴቶች መጣበሻ ክራይቴሪያ (ለወንዶች ብቻ)



[Mahi]

• • • • • •

ማስታወቂያ!!
ማስታወሻ!!
ለስራ ፈላጊዎች!!
ይሄን ያውቁ ኖራል!!
ይልሃል ባለ እድል!!!

• • • • •

"ብርዱን ኣስመልክቶ የወጣ ፍላጎትን መግለጫ"

(በፈለጉት ርእስ ማንበብ ይችላሉ)

.
ጉዳዩ:~ የፍቅር ኣጋርን መፈለግ
ፈላጊ:~እኔ
ፆታ:~ወንድ!!
እድሜ:~ከ27~34
አቋም:~ ልክ ያለው....ጡቱ ከኔ ጡት ማይበልጥ .....ኣጠገቤ ቁጭ ብሎ ወደሌላ ኣቅጣጫ እንዳላይ ማይከልለኝ....ማያሳምመኝ....

Tuesday, April 25, 2017

ኃያሉ ሠው

     


(ክቡርነታቸው)

-- ከዱሮ ጀምሮ Arrogant ናቸው - እንደ ወይራ፡፡

-- አንዳንድ እሳቤዎቻቸው አለቅጥ የተጋነኑ፣ ሆነ ብሎ ነገር ቆልማሚ እና የአሁንን (የዘመኑን) ነባራዊ እውነታ ባላየ የዘለሉ ናቸው፡፡
 
-- አሁን ላይ ያሉ መልካም መሻሻሎችን በጥቂትም  እውቅና አይሰጡም፡፡

-- አንዳንድ አቋማቸው አይመስጠኝም፣ አልስማማበትም፡፡

(ግን፣ ግን፣ ግን)

-- ክቡርነታቸው ሶስቱንም መንግስታት ወጥረውና ተጋፍጠው ሲቃወሙ ኖረዋል፡፡

-- በሰማንያ ምናምን አመት ዕድሜው ደፍሮ እውቀቱን እና እሳቤውን ሳያሰልስ የሚጽፍ ምሁር ኖሮን አያውቅም፣ የለንምም!

-- የነጮች ሎሌ፣ ወይንም የጽንፈኛው ዳያስፖራ አፈ ቀላጤ ሆነው አያውቁም፤ አሽቄ አይደሉም!!

-- የ65/66ቱን ረሃብ ቀድመው ለዓለም መንግስታት ያሳወቁትና ያጋለጡት እርሳቸው ናቸው፡፡ ጆናታን ድምቢልቢ በሳቸው ሪፖርት መሠረት ነው መጥቶ ዝነኛውን የሆረር ዶክመንተሪ የሠራው፡፡

-- ከጠረፍ ጠረፍ ዞረው መሬት ለክተው የዚህን አገር ካርታ (Atlas) ያዘጋጁ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ናቸው፡፡

-- “ጦርነት እና ነውጠኛ አብዮት ለዚህች አገር  መፍትሄ አይሆንም፣ ሆኖም አያውቅም” የሚለው ቀጥተኛ አቋማቸው ከጥንት እስካሁን አልተቀየረም፡፡ አንድ ሰው 60 አመት ሙሉ በአቋሙ ወጥ ሲሆን ማየት በራሱ ትልቅ ክላስ ነው፡፡
(መጽሃፎቻቸውንና ጽሁፎቻቸውን በሙሉ አንብበውና ፍረድ!)

-- ያልተዝረከረከ የአመንክዮ (Reasoning) አሰዳደር፣ እንዲሁም ጥልቅ ሃሳብን  በቀላል አማርኛ መግለጥ ለሳቸው የተሠጠ ትልቅ የስነጽሁፍ ክህሎት ነው፡፡ (“. . . ወይ እኔ ቂል ነኝ፣ ወይ እሱ ቂል ነው” የሚል አገላለጽ አይመስጥም?)

From Eurocentrism to Ethiocentrism

 Maimire Mennasemay (PhD)

[ Dr. Messay Kebede's thoughtful commentary on Gebrehiwot's major work, Mengistna ye Hizb Astadadar, published on this forum, draws our attention to the deleterious role that "Eurocentrism" has played in modern Ethiopia. This essay links to Messay's concern and considers what kind of perspective could restore to Ethiopians the self-confidence and creativity that have so often marked their history. ]

Monday, April 24, 2017

አሰፋ ጫቦ ቃለ መጠይቅ


አሰፋ ጫቦ - ከ'ያ ትውልድ' ብቸኛ የሚታመነው ሰው በሞት ተለየን



(ጋሽ አሰፋ ጫቦ ማን ነው?)

* * * * *

አቶ አሰፋ ጫቦ ከአባቱ ከጫቦ ሣዴ ሃማ ያሬና ከእናቱ ከማቱኬ አጀን ከተራራ አናት ላይ ከሚገኝ ሜዳማ ቦታ ላይ ጨንቻ ከተማ ነው የተወለደው፡፡ከጋሞ ሰንሰለት ተራራዋች አንዱ ጫፍ ላይ የሚገኝ ጠረጴዛ ነው ይላታል ጨንቻን ሲገልጣት  ከ2-6ኛ ክፍል እዚያው ጨንቻ የተማረ ሲሆን በዘጠኝ ዓመቱ የጨንቻ ገብርዔል ዲያቆን በመሆንም አገልግሏል በድቁናው ባገኘው ካፒታልም ጥቂት የዶሮና የበግ ግልገል ገዝቶበታል ሐሙስ ሐሙስን እየጠበቀ ኤዞ ገበያ ዶሮና እንቁላል አየነገደ ይውል ነበር ከእነሱም ውስጥ ት/ቤት ድረስ እየተከተሉ ያስቸግሩት የዶሮና የበግ ግልገልም ነበረው እንደፈረንጆቹ pet መሆናቸው ነው፡፡ የ8ኛ ክፍል ትምህርቱን በሻሸመኔ በኃላ ታሪኩን ሲያውቅ ስሙን ካላስቀየርኩ ብሎ ከታገለበት ከአጼ ናኦድ ት/ቤት ከ39 ተማሪዎች አንዱ በመሆን ነበር የተከታተለው

   የተዋቀረበትን ዋልታና ካስማ ያየበት ቆይታው በጋሞ ውስጥ ካሉ 40 ከሚሆኑ ‹ካዎ›ች አንዱ በሆኑት በዘመዱ በቀኛዝማች ኢሌታሞ ኢቻ ቤት በኖረበት ወቅት ነበር፡፡

Sunday, April 23, 2017

በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ - (አዱኛ ሌሊሳ)


(By: Adugna Lelisa Sime)

* * * * *

ወቅታዊ ጉዳዮችን የተመለከተ አጭር መግለጫ
ሚያዝያ 14 ቀን 2009ዓም
.
በቅርቡ አንዳንድ የአገራችን ክልሎች(በተለይም የኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች) የአገሪቱን ህገ መንግሥት ባልተጣረሰ መልኩ ኢኮኖሚያቸውን ለመገንባት፣አቅማቸውን ለማሳደግ እና የህዝቦቻቸውን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እያከናወኑ ያሉትን ተግባራት የሸነግ ስብስብ በትኩረት የሚመለከት እና  የሚደግፍ ቢሆንም ይህ አካሄድ በክልሎች መካከል አላስፈላጊ ፉክክር እንዳያመጣ እና አገራዊ አንድነቱን የበለጠ ስጋት ላይ የሚጥል እርምጃ እንዳይሆን ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ  ከወዲሁ አበክረን ለማሳሰብ እንወዳለን።

Remembering Prince Alemayehu

(By: Wayne Edward Maddock)

* * * * *

Remembering Prince Alemayehu: The First Ethiopian Adoptee?
.
Today is the birthdate of the late Dejazmatch Alemayehu Tewodros, born on this date on April 23, 1861.
Prince Alemayehu was the son of late Emperor Tewodros II, who ended his life by suicide on Easter Day 1868 when British forces entered his fortress in Ethiopia to rescue a group of British missionaries and diplomats.
.
Prince Alamayehu was brought to Britain under British care. Prince Alamayehu died of illness at age 18 on November 14, 1879 and was interned on the grounds of Windsor Castle .

Saturday, April 22, 2017

ትዝታ - ወ - ልጅነት

(ማሂ)

* * * * *

ኣንድ ሰፈር ነው የተወለድነው.....ቤተሰቦቻችን ጎረቤታሞች እኛ ደሞ ኣብሮኣደጎች ..... እሱዋን ለመብለጥ የማላደርገው ነገር የለም.... እቀድማታለው ከትምህርት ስንለቀቅ ቀድሜያት እቤቴ ሄጄ እራሴን የሚያክል ቂጣ ይዤ መምጫዋ መንገድ ላይ እጠብቃትና እንቁልልጭ እያልኩ ኣናዳታለው፡፡

Addis Ababa

Kebour Ghenna
(Addis Ababa: When Name and Reality Don’t Match Up)
* * * * *
By Kebour Ghenna
Translate ‘Addis Ababa’ to a foreigner and her eyes glaze over at the thought of miles of beautiful parks, boulevards and streets lined up with ornamental prune trees, and pedestrian-friendly clean neighborhoods.  Alas, the reality could not be further from the truth. 
Addis Ababa is today a dense, brutal, and crowded city, with serious deficiencies in housing, drinking water, power, sewerage, solid waste disposal, and other services. Everywhere we look, we see evidence of unthinkable inequality, deprivation and filth.

ታሪክ

(1)- (ታሪክ)
.* * * * *
መቼም ትልቅ ሠው ትልቅ ነው፡፡ ነገርን በብልሃት ያስውላል፡፡ ፍርድም ያውቃል፡፡
-
በጅሮንድ(ፊታውራሪ) ተክለ ሐዋርያት ተክለ ማርያም የ20ኛውን ክፍለዘመን የኢትዮጵያ ፖለቲካ trend እንዲህ ቀለል አድርገው በትናንሽ ዓናቅጽ ይነግሩናል፡፡
.
"የአድዋ ጦርነት ከተፈጸመ በኋላ በማግስቱ የላስታ፣ የየጁ፣ የበጌምድር፣ የጎጃም፣ የወሎ ሰዎች ፈንጥዘው ወደየአገራቸው ባቋራጭ መንገድ ጉዞ ጀመሩ፡፡ አዝማቾቻቸው ብቻቸውን ቀሩ፡፡ ሸዋ ብቻ በግድም በውድም ከአለቆቻቸው ጋር ቆዩ፡፡
ምርኮኛ ባሺቡዙክ ቀኝ እጃቸውን እና ግራ እግራቸውን እየተቆረጡ ተለቀቁ፡፡ ደም እየፈታባቸው ከሞቱት በቀር፣ እየተንፏቀቁ በየአገራቸው ገቡ፡፡ ቂማቸውን በልባቸው ውስጥ አቆይተው ግራ እጃቸውን እና ቀኙን ዱሻቸውን ባንድነት እያጋጠሙ ያጨበጭባሉ፣ ይዘፍናሉ፣ ይፎክራሉ፡፡

ግንባሩ እኛን አይወክለንም!

(Behailu Gebre Egziabiher)

* * * * *
ሰበር ዜና፦ "ግንባሩ እኛን አይወክለንም!" ሲሉ መአግ፣ ሰነግ፣ ሽነግ፣ ቁነግ፣ ሾነግ፣ ግነግ፣ ፈነግ ገለፁ።

ለዝርዝሩ ጩኸቴ ከሰፈረ ሰላም

የመሿለኪያ አንድነት ግንባር፣ የሽሮሜዳ፣ የአጣና ተራ፣ የቁጭራ ሰፈር፣ የቄራ፣ የአብነት፣ የአቧሬ፣ የካዛንቺስ፣ የሰባተኛ እንዲሁም የፈረንሳይ ነፃ አውጪ ግንባሮች ባንድ ላይ በሰጡት መግለጫ "ሸነግ እኛን አይወክለንም። አቋሙንም አንደግፍም!" ብለዋል።

ትዝታ ዘ ደርግ

ትዝታ ዘ ደርግ - ወ - የኢትዮጵያ - ኅዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ (ኢኅድሪ) - ወ የተከበሩ ጓድ መንግስቱ ኃይለ ማርያም ወልዴ፡፡
-
ደርግ ኢሰፓ ጨቋኙን ፊውዳሊዝምን ገርስሷል፡፡ መሬት ላራሹን ወጥኖ አስፈጽሟል፡፡ የመሰረተ ትምህርትን አስፋፍቷል፡፡ ለሴቶች እና ለብሄር ብሄረሰቦች ጥያቄ እውቅና ሰጥቷል፡፡ ለአገር አንድነት እስከመጨረሻው ተዋግቷል፡፡
-
(ይሄ ታሪክ የማይክደው ጥሬ ሃቅ ነው)
-
-
-
የደርግ ደካማ ጎን፣ ያደረሰው ጥፋት ላይ ብቻ አተኩር አርባ አመት ማለቃቀስ በጎ ጎኑን ሊሸፍነው አይችልም!

የሸነግ አቋም ከየት ወዴት?

(Mihretu Hanchiso)

* * * * *

የሸነግ አቋም ከየት ወዴት???
ሸነግ አሕፓና መኢሶን የወለዱት በቀይ ሽብር ጥርሱን የነቀለ ፤ በነጭ ሽብር ድርጅት የሆኖ ፓርቲ ይመስለኛል(ይኽን የመሳሰሉ ጭፍን ያለ ትርጉም እየሰጠን ከምንቸገር ድርጅቱ ታሪካዊ ምስረታው ቢገለጽልን) ።
.
.
.
ብዙ ልምድ ያለው እንደመሆኑ ነገሮችን በጥልቀት ማየት ሲገባው እንደ ጓድ ሊቀመንበሩ ስሜታዊ ይሆናል ።

የሸገር ታሪካዊ አመጣጥ

(Addisu Engidawork)

* * * * *

የሸገር ታሪካዊ አመጣጥ በመረቅኛ
1) መጀመሪያ ተጠመቅን.....
"ከዕለታት አንድ ቀን 'ጣይቱ' የተባሉ እቴጌ እዛች ፍልውሃ የምትባለው የምትጤስ ቦታ፣ እዛች እርጥብ ፊንፊኔ ገላቸውን ተታጣጥበው ጨርሰው፣ ከተቀመጡበት በርጩማ ብድግ ሲሉ፣ እንደ ደንግ የምታበራ የህልም እንቁላላቸው የምትሞቅ ግልገል ኩሬ ውስጥ ወደቀች...."

ሸነግን ከክሽፈተ እንታደገው

(Henok Yared)

ሸነግን ከክሽፈተ እንታደገው

ምንም እንኳን አስቀድመን የጀመርነውን የአራዳ ልጆች ነጻ አውጪ ግንባር ንቅናቄ እዮብ በሚባል የኡሩጉዱሩ ላቦሮ በጓሮ በር ብንነጠቀም .... ለግል ስልጣን በመሻኮት የአራዳ ልጆችን ተጋድሎ አናኮላሽም በሚል ማርስ በሚደርስ ሆደ ሰፊነት የሸነግ እንቅስቃሴ ውስጥ ለመሳተፍ ወስነናል!

ሸነግ ይጸዳል!

(Eyob Mihreteab Yohannes)

-

የፍየል ወጠጤ ልቡ ያበጠበት
እንዋጋ ብሎ ለነብር ላከበት
የማትረባ ፍየል ዘጠኝ ትወልዳለች
እነሱም ያልቃሉ እሷም ትሞታለች
. . . ብዬ የሸነግ አመራር አባሌን ማንጓጠጤ የቅርብ ጊዜ ክስተት መሆኑ አይዘነጋም፡፡

ጉድ በል ጎንደር!

ጉድ በል ጎንደር!
-
(Biniyam Habtamu)
-
ዘውዳለም ነኝ አለ ከሸገር!
ጋኖች አለቁና… አሉ ጋናውያን…
ጥያቄ ቁጥር አንድ…
እትብት ምንድን ነው? ምንድን ነው እትብት?

ያዲስ አ'ባ ልጆች!

ያዲስ አ'ባ ልጆች!

(ዘውድአለም ታደሰ)
-
-
-
ዘር እየቆጠሩ
ብሄር እየጠሩ
ሲያቅራሩ ቢውሉ ፣ አይበርደን አይሞቀን
ላ....ሽ ነው የምንለው እንዲያው ተሳስቀን።

የሸነግ ማእከላዊ ኮሚቴ የሠጠው መግለጫ

"በክቡር መተኪያ"

የታፈርክ የተከበርከው የሸነግ አባልና ደጋፊ ሆይ ድርጅትህ ከተከላካይነት ወደ አጥቂነት ተሸጋግሮልካል...

(የሸነግ ማእከላዊ ኮሚቴ የሠጠው መግለጫ)

የግፍ አገዛዝን እምቢኝ ብለው ጥቂቶች ጫካን ዱር ቤቴ ብለው ከገቡ በሁዋላ ዛሬ ሺህ ምንተሺሆችን ማሥከተል የቻለው ሸነግ ኮተቤ አካባቢ ይገኝ ከነበረ ባለ 15 ችግኝና ባለ 11 የቀረሮ ዛፍ የማዘዣ ጣብያ ወጥቶ ዛሬ ለሚገኝበት ባለ ሁለት ሺህ ላይክ ፔጅ ደርሡዋል...

Friday, April 21, 2017

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ


በአነግ (የአራዳ ልጆች ነጻ አውጪ ግንባር) የታወጀ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ

-

ዲር ጀለስካ ተንቀናል፣ተዋርደናል ብታምንም ባታምንም በቁማችን ሞተናል!
-

እኛ ሰው ባደረግናት ከተማ ጎሩጊሮጋራጌሪ ከሚባል ፓስፊክ ኦሺን በግራ ታጥፎ ካለ ሰፈር የመጣ ሰገጤ ጢባ ጢቢ ……. አንዴ እደግመዋለሁ ጢባ ጢቢ ….. ሲጫወትባት አይተን እንዳላየ እስከመቼ!

ሂሥ እና ግለ ሂሥ

ሂሥ እና ግለ ሂሥ በሸነግ ምክር ቤት...

(ክቡር መተኪያ ሀይለሚካኤል)

ባሣለፍነው ሣምንት የሸነግ ጠቅላላ ጉባኤ በአባላቱ በፖሊት ቢሮ ቊዋሚና (ቃሚና) በተጠባባቂ አባላቱ እንዲሁም በሥራ አሥፈጻሚው አባላት ላይ ሂሥና ግለ ሂሥ ሢያካሂድ በመቆየቱ እንቅሥቃሤው በሠገጤዎች የተገታ የመሠላቸው አንዳንድ በውጭ ሀገር በርገራቸውን የሚበሉና ድርጅታችንን ለማተራመሥ የሚፈልጉ ጸረ ሸነጎች ፕሮፓጋንዳ እየነዙ እንደሆን ደርሠንበታል..

ሸነግት

(እሸቱ ሃይሌ ሸነግት መንፈስ ነው ይለናል)
* * * * *
እኛ ሸነግ የሆንን የሸነግ አባል ሁሌም የምንዘመረው አንድነት ነው፡፡ ሸነግ ስትሆን ኢትዮጵያዊነት ውስጥህ ነው ሸነግ ስትሆን ፍቅር ይገዛሀል በአይን ለምታውቀው የእካባቢህ ልጅ ታክሲ ውስጥ ትከፍላለህ ወይይከፈልልሀል፡፡ ሸነጎች እንዲህ ነን፡፡ ሸነግ ማለት አንድነት አንድነትም ሸነግነት፡፡ ይሔ ዘረኝነት የእገሌ ብሔር ጭውቴ አትመቸንም፡፡ ትግራውያንን ሁሉ ወያኔ ማለት ይደብረናል፡፡ አማራን ሁሉ ነፍጠኛ ይደብረናል፡፡ የኦሮሚያን በደል ያነሳውን ሁሉ ኦነግ ማለት ይደብረናል፡፡
-
ብዙ ነገሮች ቢደብሩንም ኢትዮጵያዊነት ግን ከነ ንፍጡ እንወደዋለን፡፡ ለምን ብትሉ ሸነጎች ነና፡፡

ሸነግ ደርቢ

 ሸነግ ደርቢ

1. ሸነግ ደርቢ ዛሬ ነው :)



2. የሸነግ አባል ለሆናችሁ በሙሉ "አግ7" የሚለውን የጥምረት ስም ስታዩ ፓስዎርድ በቀላሉ እንዳይሰረቅ የተዘየደ የቃላትና የቁጥር ጥምረት መስሏችሁ እንዳትሸወዱ ይሁን :P

የሸነግ አሥርቱ ትዕዛዛት

ከወንበዴው እዮብ ምህረተአብ

( የሸነግ አሥርቱ ትዕዛዛት)
* * * * *
(1)
ሸነጋዊነት ማለት ስልጡን ማንነት፣ የከተሜያዊ ስብዕና ባለቤት መሆን ማለት ነው፡፡ ከ Regional Boundary ጋራ ንኪኪ የለውም፡፡ እንኳንስ አዲስ አበባ ተወልደህ፣ ኒውዮርክም እየኖርክ ሰገጤነት ላይፋታህ ይችላል፡፡
ሸነጋዊነትን በወንዜ ልጅ መለኪያ መመዘን በራሱ ሰገጤነት ነው፡፡

የአንቲ ሰገጤይዝም ንቅናቄ

(ሄኖክ ያሬድ)
-
የአንቲ ሰገጤይዝም ንቅናቄ “Prejudice” አልያም “stereotype” ነው እያሉ ስም ለሚያጠፉ ኮንፊውስዶች የተጻፈ እኛ የአራዳ ልጆች “ሰገጤ” ስንል “ገጠሬ” ብለው የሚያዳምጡ ተውሳኮች ተበራክተዋል፡፡ 
-
ስለዚህም “የሰገጤይዝምን” ሜታፎር ማስረዳት ግድ ብሎናል፡፡ ሰገጤ ስንል በፍጹም ገጠሬ እያልን አይደለም፡፡ አልያም የአዲስ አበባ ልጅ ያልሆነን ሁሉ ሰገጤ ብለን አልፈረጅንም፡፡ አማርኛን አኮላትፎ በጭንቀት መናገር ወይም ከነአካቴው አለመናገር ከሰገጤ ካምፕ አያስገባም፡፡ እንዲያውም የሌሎችን ቋንቋና ባህል ማክበርና ለመረዳት መሞከር የአራድነት የቴክስት ቡክ ዴፊኒሽን ነው፡፡ ስግጥና ከነአካቴው በድንበር አይፈረጅም፡፡ ዘር ቆጠራ ውስጥ ገብተን ለተወሰነ ዘር የስግጥና የሃፍረት ካባን አላለበስንም፡፡

የሸነግ አቋም

ይህ የሸነጋዊነትና የሸነግ አቋም ነው::

ከአራቱ የሃገር ምሰሶዎች አንዱ.......

(ክቡር መተኪያ ሃይለሚካኤል)

ሁሉም ሙያ በራሱ ክብር የሚሰጠውና የማይናቅ ቢሆንም በተለየ ሁኔታ ግን አራት የአንድነት አውድ ሆነው ሃገርን እንደ ድንኳን ወጥረው ያቆሙ የህልውና መሰረት የሆኑ ሙያዎች አሉ::

የሸነግ የአቋም መግለጫ

(ባለ 10 ነጥብ የሸነግ የአቋም መግለጫ)
* * * * *
(1)
ሰገጤ ሰው የሴትን ቂንጥር ይተለትላል፣ ይቆርጣል፡፡ የሴትን ብልት ሶሉ እንደተገነጠለ ጫማ ይሰፋል፡፡
(2)
ሰገጤ ሴትን ይደፍራል፣ ይጠልፋል፡፡ ይደበድባል፡፡ ያንጓጥጣል፡፡

ታላቅ ዜና

ታላቅ ዜና ለስፖርት አፍቃሪ እንዲሁም አዲስ አጀንዳ ናፋቂ ሸነጋውያን…
-
ሸነግ የነቄዎች ግንባር ነው።
ነቄዎች ደግሞ ከሰገጤ እሰጥ አገባ ቶፒኮች የፀዱ ፍተላዎችና ሙድ መያዞች በዘለለ… የሽቀላ ንፋስ አመጣሽ አጀንዳዎችን፣ ማለትም… እናት አገሬ፣ ብሄሬ፣ ሐይማኖቴ፣ እቴቴ… ወሬዎች የፀዳ ስብስብ ነው።

የሰሞኑን የፌስ ቡክ ፀዴ ሙድ መያዣ አጀንዳ እጥረት ከግምት ውስጥ በመክተት… የሸነግ ግብር ሀሌታው ሀ ግብር ከፋይ ከፍተኛ ባለሃብት አባሎች የሚሳተፉበት… ፀዴ የእግር ኳስ ቡድን ለማቋቋም እንቅስቃሴ ላይ ነን።

የሸ.ነ.ግ Business Trend Analysis Report

(ወቅታዊ የሸ.ነ.ግ Business Trend Analysis Report)
* * * * *
ገተታ በሌለው፣ በወደ ገደለው አነጋገር፡
ፊንፊኔ የኦሮሚያ መቀመጫ ከሆነች አይቀር፣ ድሪባ ኩማ የሸገር ከንቲባ ከሆነ አይቀር፣ ፊንፊኔ ዙሪያ ወደፊት መሬት ገዝተን ቤት ሰርተን ልጅ የምናሳድግበት ብቸኛው የማርያም መንገዳችን ከሆነ አይቀር (ምፅ!) (ምፅ!)
-
ብሄር አልባውና እጅግ ጸዴው፣ እግዜር እጁን ታጥቦ የሰራው የአዲስ አበባ ልጅ ከኦሮሞ Economic Revolution የድርሻውን ሊያገኝ ይገባል፡፡

የመጀመሪያይቱ

ይህ የቀልድ ሳይሆን እውነተኛ ግጥም ነው፡፡ ግጥሙን አሳትሞት፣ የዱሮው የ2004 ዓ.ም ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ ወጥቶ ነው ያነበብነው ፡፡
-
ሰገጤ ምን አይነት ዥልጥ ፍጥረት መሆኑን እርስዎ አንብበው ይፍረዱ፡፡ ይዝናኑ፡፡
-
“የመጀመሪያይቱ”
መጣች ዲሞክራሲ እንደ ሃረግ ተመዛ
ሳይበሉ ሚያጠግብ እንጀራዋን ይዛ
እንኳን ደህና መጣሽ ካለሽበት ሃገር
እኒያ ጠላቶችሽ ትቅር ብለው ነበር

ሸነግ ትለምልም!

ከሸነግ ጋር ወደፊት!! ሸነግ ትለምልም! 
(ዛፍ ናት)😀

ያሸንፋል!

*** በሜትሮፓሊታን አስተሳሰብ የነቃ፣ በሸነግ የተደራጀና፣ ፌስቡክን የታጠቀ ጀለስካ ሁሌም ያሸንፋል። ***
-
እውነት እውነት እልሃለሁ። ይህንንም ያንንም ብሄር መገንጠል፣ የፕጋፔም ይሁን የጭጋፌ ሪፐብሊክ የመመስረት ቅዠት ይኖርህ ይሆናል። ይህንን የልጅ ቅዠት ከመቃዠትህ በፊት ግን እውነተኛ የልጅነት ህልም ነበረህ። ይህ የልጅነት ህልም በብሄር፣ በሃይማኖትና በመደብ እንዲሁም በአልጋ መለያየት የማይለያይ፣ ሁሉንም ሰገጤ አንድ የሚያደርግ እውነተኛና ብቸኛ ህልም ነው። ይህ ህልም አንድና አንድ እንደሆነ አንተም እኔም እናውቀዋለን: ስናድግ የሸገር ልጅ መሆን! ይህንን ዶክተርና ፓይለት ከመሆን በበለጠ የተመኘነውን ህልም ሊያሳካ ሸነግ ተቋቁሞልናልና ባላገሮች ደስ ይበለን።

ትዝታ

(ትዝታ የአዲስ አበባ ልጅ)
* * * * *
የህዝብ ትምህርት ቤት (ዘርዓያቆብ ፣ ባልቻ ፣ አግዓዚያን ...) የተማረ ፥ ጠጠር ፣ብይ ፣ቆርኪ ተጫውቶ ያደገ፥ እቃቃ ላይ ደክሎ የሚያውቅ ፥ በፍሩት ፓንች ዴይ ፓርቲ የጨፈረ ፥ ከአዝማሪ ቤት እስከ ክለብ ሸገርን ያካለለ ፥ ድብን ብሎ ሰከሮ የሚያውቅ ፥ ቪ ኦ ኤ ፣ጀርመን፣ ኢሳት የሚከታተሉ ዘመዶች ያሉት፥ ሲጋራ አጢሶ የሚያውቅ፥ ፌስ ቡክ አካውንት ያለው፥ 24 Hours ን ሙሉ ሲዝኑን የጨረሰ ፥ በአረጋኸኝ ዘፈን ትታይ ያለ፥ ቦሌ መንገድ ወይም ብስራተ ገብርኤል አካባቢ ዎክ ያደረገ ፥ የጨረቃ ቤት የገነባ አጎት ያለው ፥ ኬር በሰራው መንገድ ላይ የተመላለሰ፥ አልሞሪካ መንፋት የሚችል ፣የአባባ ተሰፋዬን ተረት ሰምቶ ያደገ ፥ የአንበሳ አውቶብሰ ተጠቃሚ የነበረ ፥ ውይይት ላይ ተሳፍሮ ከወያላ ጋር የተጨቃጨቀ፡

ሸገር እና የሰፈር ስያሜዎቿ

(ሸገር እና የሰፈር ስያሜዎቿ)
* * * *
(ሀ)
በታላላቅ ሰዎችና አርበኞች የተሰየሙ፡
-
ራስ መኮንን ሠፈር፣ ራስ ተሰማ ሠፈር፣ ራስ ብሩ ሠፈር፣ ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ሠፈር፣ ራስ እምሩ ሰፈር፣ራስ ስዩም ሠፈር፣ ደጃዝማች ውቤ ሠፈር፣ ነጋድራስ ኃይለ ጊዮርጊስ ሠፈር ራስ ሀይሉ ሜዳ፣ደጃዝማች ዘውዱ አባኮራን ሠፈር እና ሸጎሌ (የአሶሣ ገዢ በነበሩት በሼክ ሆጀሌ አል ሐሠን የተሠየመው) ሠፈር ይጠቀሳሉ።

ሸነጋውያን

(Michael Gebre)
* * * * *
ሸገር ማለት የወደፊቷ ኢትዮጵያ ሞዴል ናት ፣ ከየትም ና ከየትም ሸገር የምታከብርህ በስራህ ና በአመለካከትህ እንጂ በማንነትህ አይደለም።
ሸነግ ደግሞ ይህንን የሸገር metropolitan ideology በሰገጤ አtመለካከት የበላይነት እንዳይሸነፍ ነፍጥ ሳይሆን mocking ን እንደ መሳርያ አንግባ የምትከላከል think tank ናት።

Adda (the Front)

Du'aan goota keenya Lt. Janaraal Jaagaama Keelloo baay'ee nu gaddisiisera. Nagaan haa boqotanii. 
-
-
-
Biyyeen isaan yaa salphaatu!
Maatii fi firoota isaanif waaqni jabina haa keennu.
Uummata Itiiyophiyaa ball'adhaaf jajabina hawwina!!
Adda (the Front)

The Buried Mirror

(Minassie Aytenfisu)
* * * * *
"People and their cultures perish in isolation, but they are born or reborn in contact with other men and women of another culture, another creed, another race. If we do not recognize our humanity in others, we shall not recognize it in ourselves." Carlos Fuentes in The Buried Mirror"

ስብ-ሰባ (ስብሰባ)

(Kuku Adem)
* * * * *
(ስብ-ሰባ(ስብሰባ) ላይ ነበርን)
-
ኪራም (የስራ ባልደረባዬ) ሁሌም ስብሰባ ልንገባ ስንል ይጸልያል....
እኔ: ኪራ ለምንድን ነው ግን ስብሰባ ከመባታችን በፊት ሁሌ የምትጸልየው?
Kiram Kebede: ቸርች ያኔ ልጅ እያለን ሁሌም ከመተኛታችሁ በፊት ጸሎት አድርጉ ተብለን ስለተማር ነዋ !

ባላገር የሚመራቸው ከተሞች

(ከስናፍቅሽ አዲስ)
* * * * *
(ባላገር የሚመራቸው ከተሞች)
-
በእርግጥ ባለሀገር አከብራለሁ፡፡ ባላገርም ቢሆን በስፍራው ሸጋና ውብ ነው፡፡ ያለ ስፍራው ሁሉም መልከ ጥፉ ስለመሆኑ ሙግት የሚገጥመኝ ያለ አይመስለኝም፡፡ ጭልጥ ያልኩ ከተሜ ነኝ ባይ በገጠር መንደሮች ውስጥ የለየለት ኋላ ቀር መሆኑን የሚነግሩት ለአኗኗሩ እንግዳነቱን የሚያሳዩ ጠባዮች ናቸው፡፡ እናም ይህቺ ሰው መደባዊ ናት እንዳትሉኝ፡፡

Ethiopian Airline DC3



(Ann Haspels)
* * * * *
You may have seen in the news where a fully paid passenger was aggressively dragged from his seat and off a United Airlines flight that was over booked. (United apologized after the filmed incident went viral.)
-
Well, when I was in high school I was on an over booked Ethiopian Airlines flight on a Boeing Jet between Egypt and Ethiopia and there was no...

ሸነግ ይነፋል

(Michael Gebre)
----
ጀለስኮች
ዶር ደርጄ ገረፋ ቱሉ ን
የ ሸነግ የክብር አባል ለማድረግ proposal ስለማቅረብ
----
ክቡር ዋና ሸይጣን ጀለስካ
እንዲሁም ከበርቴ ካቦዎች
በያላችሁበት ቅምቀማውን pause
ፅሁፌን በጥሞና ሾፍ
(ምፅፅፅፅ)(ምፅ)(ምፅ)

ሃያትን የምወዳት . . .

Leoul Zewolde
-
(ሃያትን የምወዳት . . .)
* * * * *
.
ሃ ያ ት ን የምወዳት . . . እናቴ እስኪ እንደሷ ጭዋ ልጅ ሁን ብላ በነጋ በጠባ ምሳሌ ስለምታረጋት አይደለም ። ዱምቡሉ አይኖቿ ስለሚያምሩና ሳማቸው ሳማቸው ስለሚለኝ አይደለም ። እኛ ቤት ያለው ቲቪ እኮ የናንተን ቤት እስከጎረቤታቹ ነው 'ሚያክለው እያለች ስለምታበሽቀኝና ሳኮርፍ ስለምታባብለኝ አይደለም ። አንገቷ ላይ ጥቁር ነጥብ አይቼ ሃዩ እስላም ሆና እንዴት ማርያም ሳመቻት ? ብዬ ለብዙ ግዜ ብቻዬን ስለተወዛገብኩ አይደለም ። ከላይ ሰፈር ሱቅ ፊኛ ስንገዛ 24 ቁጥርን መርጣ ግብድዬ ቀይ ፊኛ ስለደረሳት አጃጅዬ ልሰርቃት አይደለም ። ያቺ አጭርዬ የቤት ሰራተኛቸው መኮሮኒ ቀርባ በሉ አንድ ላይ ብሉ ስትለን አይ እኔ < ሰው ቤት እንዳትበላ ተብያለው > ብዬ በራሷ በሃያትዬ እጅ ደስ እያለኝ ስለምጎርስ አይደለም ።

American History X

American History X
American History X, እያንዳንዱ ዴ ሸነጋዊ ሊያየው የሚገባ፣ የኤድዋርድ ኖርተን ፀረ ሰገጤ ፊልም ነው፡፡


-


“So I guess this is where I tell you what I learned - my conclusion, right? Well, my conclusion is: Hate is baggage. Life's too short to be pissed off all the time. It's just not worth it.”

Thursday, April 20, 2017

በትልቁ መጥበብ

በትልቁ መጥበብ

(ቢኒያም ሐብታሙ)

በሁሉም ረገድ ትክክል የሆነ፣ ለአንድ ህብረተሰብ ዘለቄታዊ የፖለቲካ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ብልፅግናና ልማትን የሚያጎናፅፍ theory(ፅንሰ ሃሳብ) የለም።
አለማችን በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ Grand የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ እሳቤዎችን አስተናግዳለች።
እነዚህ Grand theories... በወቅታቸው እንደ ሃይማኖት ተሰብከው በግለሰብ ደረጃ መስዋትነትን አስከፍለው አልፈዋል።

ደብዳቤ - ለነጭ "ቺክ"

(Bethelhem Nikodimos)
-
(ደብዳቤ - ለነጭ "ቺክ")

* * * * *

በጣም ግራ ስለገባኝ ነው በበአል ምድር ይህን ደብዳቤ የምፅፍልሽ...አምስት ጥያቄዎችን ብቻ እጠይቅሻለሁ....አፋጥነሽ መልሱን ስደጅልኝ፡፡
-
1ኛ. ለአንድ ዶሮ ሆስፒታል ሙሉ ታማሚ የሚመግብ ሾርባ የሚወጣው ሽንኩርት ሁለት ቀን ሙሉ ታበስያለሽ?

(ድፎ ዳቦ፥ የከሸፈ ህብሰት)

(Nahusenay Belay)

(ድፎ ዳቦ፥ የከሸፈ ህብሰት)

* * * * *

እዉነተኛ የድፎ ዳቦ ታሪክ
ይህ በርካታ የታሪክ ድርሳናት አገላብጬ፣ እምቅ አእምሮየን ጨማምቄ የፃፍኩት እዉነተኛ ታሪክ ስለሆነ ሁሉም ሊያነበው ይገባል።

ሃይሌ ገብረስላሴ የሸነጋውያን የምንግዜም ሞዴል


ሃይሌ ገብረስላሴ የሸነጋውያን የምንግዜም ሞዴል፣ የስኬት ልኬት ጥግ ማሳያ ፍጥረት ነው፡፡ ሃይሌ እንደ ሠገጤ አለፈልኝ ብሎ አያካብድም፣ ራሱን አይቆልልም፡፡ ስራን አይንቅም፡፡ መሠረቱን አይረሳም፡፡


-


መላው የሸነግ አባላት ለሃይሌ ገብረስላሴ የመልካም ልደት ምኞታቸውን የሚገልጹት፣ እጅግ የላቀ ክብር እየተሰማቸው ነው፡፡

-

-

(መልካም ልደት፣ ሃይሌ ኬኛ!)

ሸነጋዊ ትግላችን በቀልድ

የሸነጋችን በቀልድ የተዋዛ እና ነቄ የሚመራው ይሉኝታ ለምኔ የማህበራዊ ሂስ በትውልዳችን ውስጥ ተተኪ የሌለውና የማንም የተሸማቀቀ #ሰገጤ ሊገባው የማይችል ዘመን ተሻጋሪ ፋይዳ አለው:: እንዲህ በልባዊ ድፍረት በተሞሉ የጭሶች ቀልዶች ወይም ኒዮማርክሲስት÷ኒዮአራዳ ቧልቶችን - የሸነግን (የወትሮውን ሸንጋ ሰገጤና ወጠጤ ሳይሆን) ቦቅቧቃ÷ቆሌ የራቀውን÷ከራማው የተገፈፈውን ሽንጣም (እንዲሁም ሽንታም) ጥርብ በአራዳ ጨዋታ ሳንጃ መላ የደነዘ÷ የደነዘዘ ቂጡን እየወጉ መንጨቅ አድርጎ የማንቃት ስልት ውስጥ ስላለው የኮሜዲ ጠቀሜታ ስሎቬኒያዊው ሸነግ-ቀመስ ማርክሲስት ፈላስፋ እጩ ሸነግ Slavoj Zizek የሚከተለዉን ቅልብጭና አላፊ-አግዳሚ ሰገጤ ሰርስሮት እንዲዘልቅ አድርጎ አስፍሯል፤

"Comedy is thus the very opposite of shame: shame endeavors to maintain the veil, while comedy relies on the gesture of unveiling. More closely, the comic effect proper occurs when, after the act of unveiling, one confronts the ridicule and the nullity of the unveiled content—in contrast to encountering behind the veil the terrifying Thing too traumatic for our gaze. Which is why the ultimate comical effect occurs when, after removing the mask, we confront exactly the same face as that of the mask."
...........

እናማ ሸነጋዊ ትግላችን በቀልድ ክፍለጦር እና በሰገጤ ደምሳሽ ቁምነገረኛ ጀነራሎቹ ታጅቦና አሸንግቆ (በሸነግኛ አሸብርቆ) የሰገጤ አረም እስኪያሽልብ Aluta Continua - የሸነግ መቆማያ መቀመጫ የሚያሳጡ ሽንቆጣዎች ይነፋሉ። የሰገጤም የማይነፉ (ጅን በያለበት ይንፋው!) ስግጠጣዎች እየተነፉ ይቀጥላሉ።

“በነውጠኛ አብዮት ሳይሆን፣ በማህበራዊ ለውጥ እንታመናለን!”