Friday, April 21, 2017

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ


በአነግ (የአራዳ ልጆች ነጻ አውጪ ግንባር) የታወጀ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ

-

ዲር ጀለስካ ተንቀናል፣ተዋርደናል ብታምንም ባታምንም በቁማችን ሞተናል!
-

እኛ ሰው ባደረግናት ከተማ ጎሩጊሮጋራጌሪ ከሚባል ፓስፊክ ኦሺን በግራ ታጥፎ ካለ ሰፈር የመጣ ሰገጤ ጢባ ጢቢ ……. አንዴ እደግመዋለሁ ጢባ ጢቢ ….. ሲጫወትባት አይተን እንዳላየ እስከመቼ!

ሂሥ እና ግለ ሂሥ

ሂሥ እና ግለ ሂሥ በሸነግ ምክር ቤት...

(ክቡር መተኪያ ሀይለሚካኤል)

ባሣለፍነው ሣምንት የሸነግ ጠቅላላ ጉባኤ በአባላቱ በፖሊት ቢሮ ቊዋሚና (ቃሚና) በተጠባባቂ አባላቱ እንዲሁም በሥራ አሥፈጻሚው አባላት ላይ ሂሥና ግለ ሂሥ ሢያካሂድ በመቆየቱ እንቅሥቃሤው በሠገጤዎች የተገታ የመሠላቸው አንዳንድ በውጭ ሀገር በርገራቸውን የሚበሉና ድርጅታችንን ለማተራመሥ የሚፈልጉ ጸረ ሸነጎች ፕሮፓጋንዳ እየነዙ እንደሆን ደርሠንበታል..

ሸነግት

(እሸቱ ሃይሌ ሸነግት መንፈስ ነው ይለናል)
* * * * *
እኛ ሸነግ የሆንን የሸነግ አባል ሁሌም የምንዘመረው አንድነት ነው፡፡ ሸነግ ስትሆን ኢትዮጵያዊነት ውስጥህ ነው ሸነግ ስትሆን ፍቅር ይገዛሀል በአይን ለምታውቀው የእካባቢህ ልጅ ታክሲ ውስጥ ትከፍላለህ ወይይከፈልልሀል፡፡ ሸነጎች እንዲህ ነን፡፡ ሸነግ ማለት አንድነት አንድነትም ሸነግነት፡፡ ይሔ ዘረኝነት የእገሌ ብሔር ጭውቴ አትመቸንም፡፡ ትግራውያንን ሁሉ ወያኔ ማለት ይደብረናል፡፡ አማራን ሁሉ ነፍጠኛ ይደብረናል፡፡ የኦሮሚያን በደል ያነሳውን ሁሉ ኦነግ ማለት ይደብረናል፡፡
-
ብዙ ነገሮች ቢደብሩንም ኢትዮጵያዊነት ግን ከነ ንፍጡ እንወደዋለን፡፡ ለምን ብትሉ ሸነጎች ነና፡፡

ሸነግ ደርቢ

 ሸነግ ደርቢ

1. ሸነግ ደርቢ ዛሬ ነው :)



2. የሸነግ አባል ለሆናችሁ በሙሉ "አግ7" የሚለውን የጥምረት ስም ስታዩ ፓስዎርድ በቀላሉ እንዳይሰረቅ የተዘየደ የቃላትና የቁጥር ጥምረት መስሏችሁ እንዳትሸወዱ ይሁን :P

የሸነግ አሥርቱ ትዕዛዛት

ከወንበዴው እዮብ ምህረተአብ

( የሸነግ አሥርቱ ትዕዛዛት)
* * * * *
(1)
ሸነጋዊነት ማለት ስልጡን ማንነት፣ የከተሜያዊ ስብዕና ባለቤት መሆን ማለት ነው፡፡ ከ Regional Boundary ጋራ ንኪኪ የለውም፡፡ እንኳንስ አዲስ አበባ ተወልደህ፣ ኒውዮርክም እየኖርክ ሰገጤነት ላይፋታህ ይችላል፡፡
ሸነጋዊነትን በወንዜ ልጅ መለኪያ መመዘን በራሱ ሰገጤነት ነው፡፡

የአንቲ ሰገጤይዝም ንቅናቄ

(ሄኖክ ያሬድ)
-
የአንቲ ሰገጤይዝም ንቅናቄ “Prejudice” አልያም “stereotype” ነው እያሉ ስም ለሚያጠፉ ኮንፊውስዶች የተጻፈ እኛ የአራዳ ልጆች “ሰገጤ” ስንል “ገጠሬ” ብለው የሚያዳምጡ ተውሳኮች ተበራክተዋል፡፡ 
-
ስለዚህም “የሰገጤይዝምን” ሜታፎር ማስረዳት ግድ ብሎናል፡፡ ሰገጤ ስንል በፍጹም ገጠሬ እያልን አይደለም፡፡ አልያም የአዲስ አበባ ልጅ ያልሆነን ሁሉ ሰገጤ ብለን አልፈረጅንም፡፡ አማርኛን አኮላትፎ በጭንቀት መናገር ወይም ከነአካቴው አለመናገር ከሰገጤ ካምፕ አያስገባም፡፡ እንዲያውም የሌሎችን ቋንቋና ባህል ማክበርና ለመረዳት መሞከር የአራድነት የቴክስት ቡክ ዴፊኒሽን ነው፡፡ ስግጥና ከነአካቴው በድንበር አይፈረጅም፡፡ ዘር ቆጠራ ውስጥ ገብተን ለተወሰነ ዘር የስግጥና የሃፍረት ካባን አላለበስንም፡፡

የሸነግ አቋም

ይህ የሸነጋዊነትና የሸነግ አቋም ነው::

ከአራቱ የሃገር ምሰሶዎች አንዱ.......

(ክቡር መተኪያ ሃይለሚካኤል)

ሁሉም ሙያ በራሱ ክብር የሚሰጠውና የማይናቅ ቢሆንም በተለየ ሁኔታ ግን አራት የአንድነት አውድ ሆነው ሃገርን እንደ ድንኳን ወጥረው ያቆሙ የህልውና መሰረት የሆኑ ሙያዎች አሉ::

የሸነግ የአቋም መግለጫ

(ባለ 10 ነጥብ የሸነግ የአቋም መግለጫ)
* * * * *
(1)
ሰገጤ ሰው የሴትን ቂንጥር ይተለትላል፣ ይቆርጣል፡፡ የሴትን ብልት ሶሉ እንደተገነጠለ ጫማ ይሰፋል፡፡
(2)
ሰገጤ ሴትን ይደፍራል፣ ይጠልፋል፡፡ ይደበድባል፡፡ ያንጓጥጣል፡፡

ታላቅ ዜና

ታላቅ ዜና ለስፖርት አፍቃሪ እንዲሁም አዲስ አጀንዳ ናፋቂ ሸነጋውያን…
-
ሸነግ የነቄዎች ግንባር ነው።
ነቄዎች ደግሞ ከሰገጤ እሰጥ አገባ ቶፒኮች የፀዱ ፍተላዎችና ሙድ መያዞች በዘለለ… የሽቀላ ንፋስ አመጣሽ አጀንዳዎችን፣ ማለትም… እናት አገሬ፣ ብሄሬ፣ ሐይማኖቴ፣ እቴቴ… ወሬዎች የፀዳ ስብስብ ነው።

የሰሞኑን የፌስ ቡክ ፀዴ ሙድ መያዣ አጀንዳ እጥረት ከግምት ውስጥ በመክተት… የሸነግ ግብር ሀሌታው ሀ ግብር ከፋይ ከፍተኛ ባለሃብት አባሎች የሚሳተፉበት… ፀዴ የእግር ኳስ ቡድን ለማቋቋም እንቅስቃሴ ላይ ነን።

የሸ.ነ.ግ Business Trend Analysis Report

(ወቅታዊ የሸ.ነ.ግ Business Trend Analysis Report)
* * * * *
ገተታ በሌለው፣ በወደ ገደለው አነጋገር፡
ፊንፊኔ የኦሮሚያ መቀመጫ ከሆነች አይቀር፣ ድሪባ ኩማ የሸገር ከንቲባ ከሆነ አይቀር፣ ፊንፊኔ ዙሪያ ወደፊት መሬት ገዝተን ቤት ሰርተን ልጅ የምናሳድግበት ብቸኛው የማርያም መንገዳችን ከሆነ አይቀር (ምፅ!) (ምፅ!)
-
ብሄር አልባውና እጅግ ጸዴው፣ እግዜር እጁን ታጥቦ የሰራው የአዲስ አበባ ልጅ ከኦሮሞ Economic Revolution የድርሻውን ሊያገኝ ይገባል፡፡

የመጀመሪያይቱ

ይህ የቀልድ ሳይሆን እውነተኛ ግጥም ነው፡፡ ግጥሙን አሳትሞት፣ የዱሮው የ2004 ዓ.ም ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ ወጥቶ ነው ያነበብነው ፡፡
-
ሰገጤ ምን አይነት ዥልጥ ፍጥረት መሆኑን እርስዎ አንብበው ይፍረዱ፡፡ ይዝናኑ፡፡
-
“የመጀመሪያይቱ”
መጣች ዲሞክራሲ እንደ ሃረግ ተመዛ
ሳይበሉ ሚያጠግብ እንጀራዋን ይዛ
እንኳን ደህና መጣሽ ካለሽበት ሃገር
እኒያ ጠላቶችሽ ትቅር ብለው ነበር

ሸነግ ትለምልም!

ከሸነግ ጋር ወደፊት!! ሸነግ ትለምልም! 
(ዛፍ ናት)😀

ያሸንፋል!

*** በሜትሮፓሊታን አስተሳሰብ የነቃ፣ በሸነግ የተደራጀና፣ ፌስቡክን የታጠቀ ጀለስካ ሁሌም ያሸንፋል። ***
-
እውነት እውነት እልሃለሁ። ይህንንም ያንንም ብሄር መገንጠል፣ የፕጋፔም ይሁን የጭጋፌ ሪፐብሊክ የመመስረት ቅዠት ይኖርህ ይሆናል። ይህንን የልጅ ቅዠት ከመቃዠትህ በፊት ግን እውነተኛ የልጅነት ህልም ነበረህ። ይህ የልጅነት ህልም በብሄር፣ በሃይማኖትና በመደብ እንዲሁም በአልጋ መለያየት የማይለያይ፣ ሁሉንም ሰገጤ አንድ የሚያደርግ እውነተኛና ብቸኛ ህልም ነው። ይህ ህልም አንድና አንድ እንደሆነ አንተም እኔም እናውቀዋለን: ስናድግ የሸገር ልጅ መሆን! ይህንን ዶክተርና ፓይለት ከመሆን በበለጠ የተመኘነውን ህልም ሊያሳካ ሸነግ ተቋቁሞልናልና ባላገሮች ደስ ይበለን።

ትዝታ

(ትዝታ የአዲስ አበባ ልጅ)
* * * * *
የህዝብ ትምህርት ቤት (ዘርዓያቆብ ፣ ባልቻ ፣ አግዓዚያን ...) የተማረ ፥ ጠጠር ፣ብይ ፣ቆርኪ ተጫውቶ ያደገ፥ እቃቃ ላይ ደክሎ የሚያውቅ ፥ በፍሩት ፓንች ዴይ ፓርቲ የጨፈረ ፥ ከአዝማሪ ቤት እስከ ክለብ ሸገርን ያካለለ ፥ ድብን ብሎ ሰከሮ የሚያውቅ ፥ ቪ ኦ ኤ ፣ጀርመን፣ ኢሳት የሚከታተሉ ዘመዶች ያሉት፥ ሲጋራ አጢሶ የሚያውቅ፥ ፌስ ቡክ አካውንት ያለው፥ 24 Hours ን ሙሉ ሲዝኑን የጨረሰ ፥ በአረጋኸኝ ዘፈን ትታይ ያለ፥ ቦሌ መንገድ ወይም ብስራተ ገብርኤል አካባቢ ዎክ ያደረገ ፥ የጨረቃ ቤት የገነባ አጎት ያለው ፥ ኬር በሰራው መንገድ ላይ የተመላለሰ፥ አልሞሪካ መንፋት የሚችል ፣የአባባ ተሰፋዬን ተረት ሰምቶ ያደገ ፥ የአንበሳ አውቶብሰ ተጠቃሚ የነበረ ፥ ውይይት ላይ ተሳፍሮ ከወያላ ጋር የተጨቃጨቀ፡

ሸገር እና የሰፈር ስያሜዎቿ

(ሸገር እና የሰፈር ስያሜዎቿ)
* * * *
(ሀ)
በታላላቅ ሰዎችና አርበኞች የተሰየሙ፡
-
ራስ መኮንን ሠፈር፣ ራስ ተሰማ ሠፈር፣ ራስ ብሩ ሠፈር፣ ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ሠፈር፣ ራስ እምሩ ሰፈር፣ራስ ስዩም ሠፈር፣ ደጃዝማች ውቤ ሠፈር፣ ነጋድራስ ኃይለ ጊዮርጊስ ሠፈር ራስ ሀይሉ ሜዳ፣ደጃዝማች ዘውዱ አባኮራን ሠፈር እና ሸጎሌ (የአሶሣ ገዢ በነበሩት በሼክ ሆጀሌ አል ሐሠን የተሠየመው) ሠፈር ይጠቀሳሉ።

ሸነጋውያን

(Michael Gebre)
* * * * *
ሸገር ማለት የወደፊቷ ኢትዮጵያ ሞዴል ናት ፣ ከየትም ና ከየትም ሸገር የምታከብርህ በስራህ ና በአመለካከትህ እንጂ በማንነትህ አይደለም።
ሸነግ ደግሞ ይህንን የሸገር metropolitan ideology በሰገጤ አtመለካከት የበላይነት እንዳይሸነፍ ነፍጥ ሳይሆን mocking ን እንደ መሳርያ አንግባ የምትከላከል think tank ናት።

Adda (the Front)

Du'aan goota keenya Lt. Janaraal Jaagaama Keelloo baay'ee nu gaddisiisera. Nagaan haa boqotanii. 
-
-
-
Biyyeen isaan yaa salphaatu!
Maatii fi firoota isaanif waaqni jabina haa keennu.
Uummata Itiiyophiyaa ball'adhaaf jajabina hawwina!!
Adda (the Front)

The Buried Mirror

(Minassie Aytenfisu)
* * * * *
"People and their cultures perish in isolation, but they are born or reborn in contact with other men and women of another culture, another creed, another race. If we do not recognize our humanity in others, we shall not recognize it in ourselves." Carlos Fuentes in The Buried Mirror"

ስብ-ሰባ (ስብሰባ)

(Kuku Adem)
* * * * *
(ስብ-ሰባ(ስብሰባ) ላይ ነበርን)
-
ኪራም (የስራ ባልደረባዬ) ሁሌም ስብሰባ ልንገባ ስንል ይጸልያል....
እኔ: ኪራ ለምንድን ነው ግን ስብሰባ ከመባታችን በፊት ሁሌ የምትጸልየው?
Kiram Kebede: ቸርች ያኔ ልጅ እያለን ሁሌም ከመተኛታችሁ በፊት ጸሎት አድርጉ ተብለን ስለተማር ነዋ !

ባላገር የሚመራቸው ከተሞች

(ከስናፍቅሽ አዲስ)
* * * * *
(ባላገር የሚመራቸው ከተሞች)
-
በእርግጥ ባለሀገር አከብራለሁ፡፡ ባላገርም ቢሆን በስፍራው ሸጋና ውብ ነው፡፡ ያለ ስፍራው ሁሉም መልከ ጥፉ ስለመሆኑ ሙግት የሚገጥመኝ ያለ አይመስለኝም፡፡ ጭልጥ ያልኩ ከተሜ ነኝ ባይ በገጠር መንደሮች ውስጥ የለየለት ኋላ ቀር መሆኑን የሚነግሩት ለአኗኗሩ እንግዳነቱን የሚያሳዩ ጠባዮች ናቸው፡፡ እናም ይህቺ ሰው መደባዊ ናት እንዳትሉኝ፡፡

Ethiopian Airline DC3



(Ann Haspels)
* * * * *
You may have seen in the news where a fully paid passenger was aggressively dragged from his seat and off a United Airlines flight that was over booked. (United apologized after the filmed incident went viral.)
-
Well, when I was in high school I was on an over booked Ethiopian Airlines flight on a Boeing Jet between Egypt and Ethiopia and there was no...

ሸነግ ይነፋል

(Michael Gebre)
----
ጀለስኮች
ዶር ደርጄ ገረፋ ቱሉ ን
የ ሸነግ የክብር አባል ለማድረግ proposal ስለማቅረብ
----
ክቡር ዋና ሸይጣን ጀለስካ
እንዲሁም ከበርቴ ካቦዎች
በያላችሁበት ቅምቀማውን pause
ፅሁፌን በጥሞና ሾፍ
(ምፅፅፅፅ)(ምፅ)(ምፅ)

ሃያትን የምወዳት . . .

Leoul Zewolde
-
(ሃያትን የምወዳት . . .)
* * * * *
.
ሃ ያ ት ን የምወዳት . . . እናቴ እስኪ እንደሷ ጭዋ ልጅ ሁን ብላ በነጋ በጠባ ምሳሌ ስለምታረጋት አይደለም ። ዱምቡሉ አይኖቿ ስለሚያምሩና ሳማቸው ሳማቸው ስለሚለኝ አይደለም ። እኛ ቤት ያለው ቲቪ እኮ የናንተን ቤት እስከጎረቤታቹ ነው 'ሚያክለው እያለች ስለምታበሽቀኝና ሳኮርፍ ስለምታባብለኝ አይደለም ። አንገቷ ላይ ጥቁር ነጥብ አይቼ ሃዩ እስላም ሆና እንዴት ማርያም ሳመቻት ? ብዬ ለብዙ ግዜ ብቻዬን ስለተወዛገብኩ አይደለም ። ከላይ ሰፈር ሱቅ ፊኛ ስንገዛ 24 ቁጥርን መርጣ ግብድዬ ቀይ ፊኛ ስለደረሳት አጃጅዬ ልሰርቃት አይደለም ። ያቺ አጭርዬ የቤት ሰራተኛቸው መኮሮኒ ቀርባ በሉ አንድ ላይ ብሉ ስትለን አይ እኔ < ሰው ቤት እንዳትበላ ተብያለው > ብዬ በራሷ በሃያትዬ እጅ ደስ እያለኝ ስለምጎርስ አይደለም ።

American History X

American History X
American History X, እያንዳንዱ ዴ ሸነጋዊ ሊያየው የሚገባ፣ የኤድዋርድ ኖርተን ፀረ ሰገጤ ፊልም ነው፡፡


-


“So I guess this is where I tell you what I learned - my conclusion, right? Well, my conclusion is: Hate is baggage. Life's too short to be pissed off all the time. It's just not worth it.”

“በነውጠኛ አብዮት ሳይሆን፣ በማህበራዊ ለውጥ እንታመናለን!”